ቅዱስ አባታችን ፍራንቸስኮ እና የሞስኮና የመላው ሩስያ ፓትርያርክ ክሪል በጋር ያወጡትን 30 አንቀጽ ያለውን የጋራ መግለጫ እንደ
እንደምከተለው አጠቃለን አቅርበነዋል።
የጌታች የኢየሱስ ፀጋ የእግዚአብሔር ፍቅር እና የመንፈስ ቅዱስ አንድነት ከሁላችሁም ጋር ይሁን። 2ቆሮ 13፡14
- ከአንቀጽ 1-3 የተሰጠው መግለጫ ትኩረቱን ያደረገው ሁለቱ የቤተ ክርስትያን መሪዎች በኩባ ያደርጉትን ታሪካዊ የፊት ለፊት
ግንኙነት አድንቆና ለአዘጋጆቹ ምስጋናን ችሮ አሁን በምንኖርበት ዘመን ከፍተኛ ተርጉም ያለው ግንኙነተ መሆኑን አመልክቷል።
- ከአንቀጽ 4-7፣ የካቶሊክና የኦርቶዶክስ ቤተ ክርስትያንን ታሪካዊ ግንኙነትን ከግምት በማስገባት በተለይም ደግሞ አንድ በነበሩበት
ወቅት እና በ1054 የተለያዩበት ምክንያት “በጊዜው በነበሩ ሰዎች ድክመት እና ሓጥያት” ምክንያት መሆኑን አውስቶ ሁል ጊዜ የኢየሱስ
ክርስቶስ ጸሎት የነበረው “ሁሉም አንድ ይሆኑ ዘንድ” በመሆኑ አሁን ለአንድነት የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ መቀጠልና ልዩነቶችን በንግግር
ማጥበብ እንድምገባው የምያወሳ ነው።
- ከአንቀጽ 8-12 ትኩረቱን ያደረገው በመካከለኛው ምስራቅ እና በአፍሪካ በክርስትያኖች ላይ እየተደረግ ያለውን ስቃይ እና መከራን
ትኩረት በመስጠት በተለይም ደግሞ በዝህ አሰቃቂ ሰደት እና መከራ ክርስትያን በመሆናቸው ምክንያት ብቻ ሕይወታቸውን ያጡትን ክርስትያኖች
“በእምነታቸው የጸኑ ሰማዕታት” መሆናቸውን በማዋሳት ክርስትያኖች ሁሉ በእብረት ይህንን አሰቃቂ ስደት እና መከራ ለማስቆም በአንድነት
እድቆሙ የምያሳስብ ነው።
- አንቀጽ 13፤ በአይማኖት ተቋማት መካከክል የምደረገውን ገንቢ ውይይት አስፈላጊነትን በማስመር ምንም አይነት ጥላቻ እና ግድያ
በአንዱ በእግዚአብሔር ስም መደረግ እንደ ሌለበት የምያሳስብ ነው።
- ከአንቀጽ 14-16፣ በአይማኖት ነፃነት ላይ የተደቀነውን ከፍተኛ አደጋ በማውሳት በተለይም የተለያዩ የአውሮፓ ሀገራት የአይማኖትን
ነፃነት የምፈታተኑ አስገዳጅ ውሳኔዎችን እየወሰኑ የክርስትያን ማህበረሰብን መብት እየተጋፉ በመሆናቸው ከዝህ ድርጊታቸው እንድታቀቡ
የምጠይቅ እና በተለይም የአውሮፓ አሀጉር ሥር መሰረት የሆነውና በአሁኑ ጊዜ በስደንጋጭ ሁኔታ እየተረሳና ትኩረት እየተነፈገው የመጣውን
የክርስትና እምነት ትኩረት እንዲሰጠው የምያሳስብ ነው።
- ከአንቀጽ 17-18፣ ትኩረቱን ያደረገው በአሁኑ ወቅት በአለማችን በስቃይ፣ በመከራ፣ በድህነትና በጦርነት እንድሁም በስደት
የምገኙትን የማሕበረስብ ክፍሎችን የምለከት እና የአለም ሀያላን ሀገሮች ቁዋሚ መፍትሄ እንድያበጁ ጥሪ የምያቀርብ ነው።
- ከአንቀጽ 19-21 የምያተኩረው በቤተሰብ ሕይወት ዙሪያ፣ በተልይም ጋብቻ በአንድ ወንድ እና ሴት መካከል በታልቅ ፍቅር የምፈጠር
መሆኑን በማውሳት ነገር ግና አሁን ባለንበት ዘመን ይህ ታላቅ የጋብቻ ተርጉም እና ምስጢር መልኩን እየቀየር በመምጣቱ የምያስከትለው
ሰባዊ ቀውስ ከባድ በመሆኑ ክርስታያኖች በመረዳት መጻሓፍ ቅዱሳችን የምያዘንን የጋብቻ ትክክለኛ ትርጉም በተግባር በማዋል እና ማንኛውንም
የዝህ ተቃራኒ የሆነውን ሓሳብ መቃወም እናዳለባቸው በማውሳትና ለሰው ልጅ ሕይወት ክብር እንድሰጥ የምያሳስብ ነው።
- ከአንቀጽ 22-23፡ የምያተኩረው በወጣቶች ላይ ስሆን የወጣቱ ተውልድ ከእግዚአብሔር የተሰጠውን ታላቅ ችሎታ በማቴ. 25፣25
እንድተገለጸው፣ የተሰጠን ፍሬ እንድያፈራ በመሆኑ የተሰጣችሁን መንፈሳዊ ፀጋ እና ችሎታ ቅዱስ ወንጌላችን በምያዘን መልኩ በመተግበር
ለሰላም፣ ለእውነት እና ለፍትህ በመስራት የእግዚአብሔርን ክበር በአለም ልመስክሩ እንደምገባ የምያሳስብ ነው።
- ከአንቀጽ 24-27 ያተኮረው በካኦቶሊክና በኦርቶዶክስ አብያተ ክርስትያናት መካከል የምታየውን ውጥረት የተመለከተ ስሆን በተለይም
ከአንዱ እምነት ወደ ሌላው ሰዎችን ለመሳብ የምደረገውን ሙከራ የተመለከተ፣ እንድሁም የስበከተ ወንጌል አገልግሎት አንዱ በለላው ክልል
በማግባት መፈጸምንና የምስራቅ አውሮፓ ክርስትያኖች ጉዳይ የምፈጸመውን ጣልቃ ገብነትና በተልይም የዩክሬይንን ጉዳይ የዳሰሰ ነው።
- አንቀጽ 28፣ የምያተኩረው አሁን ያለንበት አለም የተቀናጀ ምስክርነት የምፈልግ በመሆኑ የውደፊቱ የአልም ሕዝብ ህልውና የተመሰረተው
አሁን እኛ በምንሰጠው ምስክርነት ላይ መሰርት አድርጎ በመሆኑ በዝህ በአስቸጋሪ ወቅት ሕብረትን በመፍጠር የእውነትን መንፈስን ሳንሰላች
ልንመስክር ያስፈልጋል።
- ከአንቀጽ 29-30 የምመለከተው በክርስቶስ ላይ ተስፋችንን በመጣልና እናታችን ቅድስት ድንግል ማሪያም ለምያከብሩዋት ሁሉ የምትማጸን
በመሆኑዋ፣ በዝህ በመተማመን እግዚአብሔር በፈቀደ ቀን እና ሰአት፣ አንደ ገና እንዝህ እህት አብያተ ክርስትያናት አንድ እንደምሆኑ
ተስፋ በማድረግ ለአለም አንድነት እና ሰላም አንድሁም ለእግዚአብሔር ሕዝቦች ህልውናና ለእግዚአብሔር ክብር፣ ቅዱስና ለማይነጣጠልው
ቅድስት ስላሴ አደራ በመስጠት የአቁዋም መግለጫው ተጠናቁዋል።